የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ባሉት ክፍት የስራ መደቦች ብቁ ባለሙያዎችን አወዳድሮ ለመቅጠር ከዚህ ቀደም ምዝገባ ማከናወኑ ይታወቃል፡፡
ስለሆነም እሁድ መጋቢት 14፣ 2017 ዓ.ም ከሰዓት 7:30 በአዲስ አበባና ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር እንዲሁም በሁሉም ክልሎች ዋና ከተማ ፈተና የሚሰጥ ስለሆነ ለፅሁፍ ፈተና ያለፋችሁ ስም ዝርዝራችሁን ከዚህ በታች የገለፅን መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
ጥብቅ ማሳሰቢያ፡-
- ለፈተና የተመረጠው በመጀመሪያ ዲግሪ የተመዘገቡትን ሲሆን በዲፕሎማና በሌብል የተመዘገባችሁ ወደፊት የምናሳውቅ ይሆናል።
- ፈተናው ጠዋት 2:30 ከሰአት 7:30 የሚጀምር ሲሆን በሰአቱ የአልተገኘ ተፈታኝ የማናስተናግድ መሆኑን እንገልፃለን።
- ማንነታችሁን የሚገልጽ መታወቂያ መያዝ ይጠበቅባችኋል።
- ማንኛውንም ኤሌክትሮኒክስ ዕቃ /ስልክ / ይዞ መግባት አይፈቀድም
- የስም ዝርዝራችሁ ካለበት ቦታ ውጭ ቦታ ቀይሮ መፈተን አይቻልም።
