በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የተደረጉ የኢሚግሬሽን አገልግሎት ማሻሻያዎች እና ለአፍሪካ ህብረት ጉባኤ የተደረገ ዝግጅት

የኢትዮጵያ ኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የሚሰጠውን የአየር ድንበር ቁጥጥር አገልግሎት በዘመናዊ ቴክኖሎጂ እና በሰለጠነ የሰው ኃይል ማሻሻሉን አስታወቀ። ተቋሙ በተለይም በመጪው ሳምንት በአዲስ አበባ ለሚካሄደው 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ እንግዶችን በብቃት ለመቀበል ከፍተኛ ዝግጅት ማድረጉን ገልጿል።