የሰንደቅ ዓላማ ቀን በኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ተከበረ።

ጥቅምት 4/2017 ዓ.ም  17ኛው ብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀን  በኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ቅጥር ጊቢ ውስጥ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት በተገኙበት በተቋሙ አመራሮች፣ ሠራተኞችና ተገልጋዮች በደማቅ ሁኔታ በዓሉ ተከብሯል።

ዕለቱ “ሰንደቅ ዓላማችን ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ከፍታ” በሚል መሪ ሐሳብ በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከበረ ይገኛል።

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት