ለ20ኛው የዓለም የሥራ ድርጅት አህጉራዊ ጉባኤ መሳካት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት የእውቅና ስነ-ስርዓት ተካሄደ።

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 27፣ 2017 

ለ20ኛው የዓለም የሥራ ድርጅት አህጉራዊ ጉባኤ መሳካት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት የእውቅና ስነ-ስርዓት በትላንትናው ምሽት በኢንተር-ሌግዤሪ ሆቴል ተካሂዷል፡፡

በዚህም ኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ከ2000 በላይ እንግዶች እና 30 ሚኒስትሮችን የቪዛ እና የኢሚግሬሽን አገልግሎት  በተቀላጠፈ  መንገድ በመስጠት አህጉራዊ ጉባኤው  በስኬት እንዲጠናቀቅ ላበረከተው አስተዋፅኦ የእውቅና ሽልማት ተበርክቶለታል፡፡