የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ከፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን እና ከልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 አስተዳደር ጋር በመቀናጀት በተደረገ ልዩ ኦፕሬሽን በተቋሙ ቢሮ አካባቢ በመሆን በህገ ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ 65 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር አዋለ።







ተጠርጣሪዎች በተለያየ የህገ-ወጥ የድለላ ስራዎች ላይ የተሰማሩ፣ የስራ ከባቢውን በማወክ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ችግር እየፈጠሩ ያሉ፣ በተለያየ የማጭበርበር እና የማታለል ተግባር ላይ ተሰማርተው የነበሩ እና በህገ-ወጥ መንገድ የኦን ላይን የአስቸኳይ ፓስፖርት የሚሞሉ መሆናቸው ተገልፆል።
በአጠቃላይ 7 በህገወጥ የንግድ እንቅስቃሴ ላይ የተሰማሩ ቤቶች መታሸጋቸውን እና 65 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር የዋሉ መሆኑ ተነግሯል። ከእነዚህም መካከል 25 ቱ ሴቶች እንደሆኑ ታውቋል።
የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት
Telegram: https://t.me/ICS_Ethiopia
Facebook: https://www.facebook.com/ICSEthiopia
Twitter: https://twitter.com/ics_ethiopia
TikTok: https://www.tiktok.com/@ics_ethiopia
