በህገ ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ 65 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ።

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ከፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን እና ከልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 አስተዳደር ጋር በመቀናጀት በተደረገ ልዩ ኦፕሬሽን በተቋሙ ቢሮ አካባቢ በመሆን በህገ ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ 65 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር አዋለ።

ተጠርጣሪዎች በተለያየ የህገ-ወጥ የድለላ ስራዎች ላይ የተሰማሩ፣ የስራ ከባቢውን በማወክ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ችግር እየፈጠሩ ያሉ፣ በተለያየ የማጭበርበር እና የማታለል ተግባር ላይ ተሰማርተው የነበሩ እና በህገ-ወጥ መንገድ የኦን ላይን የአስቸኳይ ፓስፖርት የሚሞሉ መሆናቸው ተገልፆል።

በአጠቃላይ 7 በህገወጥ የንግድ እንቅስቃሴ ላይ የተሰማሩ ቤቶች መታሸጋቸውን እና 65 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር የዋሉ መሆኑ ተነግሯል። ከእነዚህም መካከል 25 ቱ ሴቶች እንደሆኑ ታውቋል።

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት

Telegram: https://t.me/ICS_Ethiopia

Facebook: https://www.facebook.com/ICSEthiopia

Twitter: https://twitter.com/ics_ethiopia

TikTok: https://www.tiktok.com/@ics_ethiopia

LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/icsethiopia

YouTube: https://www.youtube.com/@Ics_Ethiopia

Latest Posts

Any Questions?

Call us!

8133