በእስቶፕ ኦቨር ቱሪዝም ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተካሄደ

ሰኔ 16 ፣ 2018 ዓ.ም የሀገሪቱን የቱሪዝም ዘርፍ ለማሳደግ ይፋ በሆነው እስቶፕ ኦቨር ቱሪዝም ቪዛ ዙሪያ ከቱሪዝም ሚንስቴር ፣ አየር መንገድ እና ኢንሳ ከተውጣጡ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተካሄዷል።

በውይይቱ የቪዛ አሰራር ቴክኖሎጂ ልህቀትን በስራ ላይ ማዋል እና በቅንጅት በሚሰሩ ስራዎች ዙሪያ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።

ከቱሪዝም ሚንስቴር ጋር በመተባበር የሚተገበረው አሰራሩ በሀገሪቱ የቱሪዝም አድገት ላይ ትልቅ ሚና እንደሚኖረው ይጠበቃል።

በውይይቱ ላይ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬከተር ክብርት ወይዘሮ ሰላማዊት ዳዊት ፣ የቱሪዝም ሚንስትር ሚንስቴር ዳኤታ የሆኑት ዶክተር እንዳገና አበበን ጨምሮ የአየር መንገድ እና የኢንሳ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት

ሁሉም የሚታወቅባት ኢትዮጵያ !

————————

ለበለጠ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ድህረ -ገፆችንን ይጎብኙ ይወዳጁን ……

Telegram: https://t.me/ICS_Ethiopia

Facebook: https://www.facebook.com/ICSEthiopia

Twitter: https://twitter.com/ics_ethiopia

TikTok: https://www.tiktok.com/@ics_ethiopia

LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/icsethiopia

YouTube: https://www.youtube.com/@Ics_Ethiopia

Instagram: https://www.instagram.com/icsethiopia/